ስልክ፡ 011-1-23-35-18 / 011-1-23-35-15
Click here to add your own text
Click here to add your own text
ይህ ቲያትር ሙሉ ገቢው ለካቴድራሉ እድሳት ስለሆነ ሁሉም ሰው ሼር ያድርገው፡፡ በተጠቀሱት ቀናትም ይህንን በአይነቱ ለየት ያለውን ትውፊታዊ ቲያትር በመመልከት እውቀትዎን ያሳድጉ፡፡
Click here to add your own text
Click here to add your own text
የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የ2008 ዓ.ም የፋሲካ በዓልን ምክንያት በማድረግ ለበርካታ ችግረኞች ታላቅ የምሳ ግብዣ አደረገላቸው!!
በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሥር የሚገኘው የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል እሑድ ሚያዚያ 30 ቀን 2008 ዓ.ም ቁጥራቸው ከ1,000 በላይ ለሚሆኑ ነዳያን /ችግረኞች ሰፊ የሆነ የምሳ ግብዣ ያደረገላቸው መሆኑን የዝግጅት ክፍላችን ከቦታው ድረስ በመሄድ አረጋግጧል፡፡ ይህ ታላቅ የምሳ ግብዣ የተከናወነበት ቦታ ቀደም ሲል በነገሥታቱ፣ በመሳፍንቱ፣ በመኳንንቱና በደጅአዝማቾቹ ዘመን በተመሠረተውና 107 ዓመት እድሜ ባስቆጠረው የካቴድራሉ የሰንበቴ […]
የግብረ ሰላም በዓል በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በድምቀት ተከበረ
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣ ብፁዓን ሊቃነ ጳጰሳት፣ የጠቅላይ ቤተ ክህነት የመምሪያ ኃላፊዎች፤የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስከያጅና የክፍል ኃላፊዎች፣ የአዲስ አበባ ገዳማትና አድባራት የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች በተገኙበት ቅዳሜ ሚያዝያ 22 ቀን 2008 ዓ.ም የግብረ ሰላም በዓል በታላቅ ድምቀት ተከብሯል፡፡ወለመልአከ ሕይወትሰ ሰቀልዎ ለዘተንስአ […]
ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተገኝተው የጸሎተ ሐሙስን በዓል አከበሩ
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ተክለሃይማኖት ሐሙስ ሚያዝያ 20 ቀን 2008 ዓ.ም በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ከብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ጋር በመገኘት በካቴድራሉ ለተገኘው በርካታ ምዕመናን አባታዊ ትምህርት እና ቃለ ምዕዳን አስተላልፈዋል፡፡ በአስተላለፉት አባታዊ ትምህርት ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በጸሎተ ሐሙስ የደቀ መዛሙርቱን እግር በማጠብ ሥርዓተ […]
“ሰሙነ ሕማማት”
“ነሥአ ደዌነ መጾረ ሕማመነ በእውነት ደዌያችንን ተቀበለ፣ ሕማማችንን ተሸከመ፣ ስለመተላለፋችን ቆሰለ፣ በእርሱም ቍስል እኛ ተፈወስን” (ኢሳ. 53÷4-6) በማለት ነቢዩ ኢሳይያስ የተነበየው ትንቢት ይፈጸም ዘንድ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እኛን ከፍዳና ከዘለዓለማዊ ሞት ለማዳንና ከዲያብሎስም ቁራኝነት ነፃ ለመውጣት ሲል 13ቱን ሕማማተ መስቀልና ሌሎቹንም ጸዋትወ መከራዎች የተቀበለበት ሳምንት “ሰሙነ ሕማማት” በመባል ይታወቃል፡፡ ትርጓሜውም የመከራ ሳምንት ማለት ነው፡፡ […]
በመንበረ ጸባዖት ቅ/ሥላሴ ካቴድራል የካህናት ሙያ ማሻሻያ ሥልጠና ተካሄደ
የካቴድራሉ ስብከተ ወንጌል ክፍል ከካቴድራሉ ሰ/ጉ/አስተዳደር ጋር በመሆን ቀደም ብሎ በያዘው ዕቅድ መሠረት ከየከታቲት 1 ቀን ጀምሮ ለሁለት ሳምንታት ያህል • በትምህርተ ሃይማኖት• በመጽሐፍ ቅዱስ• በትምህርተ ኖሎት• ስለቤተ ክርስቲያን አስተዳደር• ስለ ስብከት ዘዴ አቀራረብ በተመለከተ ከ32 በላይ ለሆኑ መደበኛ ካህናት ሥልጠናው የተሰጠ ሲሆን ሠልጣኞቹ በሥልጠናው ያገኙት ግንዛቤ እራሳቸውን በሁሉም ሙያ በማብቃት መልካም የሆነ ክህነታዊ አገልግሎት […]